Monday, December 8, 2014

ESAT Bezhisamint Dr Tadese Biru & Ermias Legesse December 2014 | ESATTUBE

ESAT Bezhisamint Dr Tadese Biru & Ermias Legesse December 2014 | ESATTUBE

Breaking News: 70 Ethiopian migrants drown off Red Sea coast of Yemen

December 7, 2014
(Reuters) – At least 70 Ethiopians drowned when a boat used by smugglers to transport illegal migrants to Yemen sank in the Red Sea in rough weather, security authorities in the western part of the country said on Sunday.Ethiopian migrants drown off Red Sea coast of Yemen
Human traffickers often use unseaworthy boats to smuggle African migrants to Yemen, seen as a gateway to wealthier parts of the Middle East, such as Saudi Arabia and Oman, and the West.
Security authorities in Taiz province said the small boat sank on Saturday due to high winds and rough seas off the country’s al-Makha port.
They said the boat was carrying 70 people, all of them Ethiopians.
Tens of thousands of migrants from Africa, the Middle East and beyond crowd into often unsafe boats each year and many drown.
In March, at least 42 illegal African migrants drowned in the Arabian Sea off the southern coast of Yemen.
source ECADF 

Friday, November 28, 2014

የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌ የወጣቶች ክፍል አዘጋጅነት ታላቅ ሰላማዊሰልፍ በኖርዌይ ኦስሎ ተካሄደ!!!

የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌ የወጣቶች ክፍል አዘጋጅነት በዛሬው እለት ሀሙስ (November 27,2014)  በኖርዌ ኦስሎ በእንግሊዝ ኢንባሲ ፊት በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከሩቅም ከቅርብም በአንድነት በመሰባሰብ ከቀኑ 13፡30 እስከ 15፡00 ስዓት ታላቅ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ አካሄዱ።
DSC_0233DSC_0220DSC_0268DSC_0230
የሰልፉ ዋና አላማ የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሃፊና የሰባዊ መብት ተቆርቋሪ የሆኑት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ  በአንምባ ገነኑ የወያኔ ቡድን በህገ ወጥ መንገድ ታፍነውና ፍትህ ተነፍገው በእስር ቤት መታሰራቸውን ለመቃወም ሲሆን በሰልፉ ስፍራ የተገኙ ሰዎች ሁሉ አቶ አንዳርጋቸው ለዲሞክራሲ እና ሰብአዊ መብት መከበር ከወጣትነት ጀምሮ የታገለ ታላቅ የሰላም ምሳሌ፣ የፍትህ ተምሳሌት፣ የነጻነት በር ከፋች እንዲሁም አገራዊ ስሜት የተላበሰ አርበኛ እንጂ እስር፣ ድብደባና መሰቃየት የሚገባው ሰው አልነበረም በማለት ለእንግሊዝ መንግስት በኢንባሲው አማካኝነት ዜጋዋን ከአረመኔና ጨካኝ መዳፍ እንድትታደግና ፍትህ እንዲያገኝ  በከፍተኛ ድምጽ አሳስበዋል።
ወጣቶች እጃቸውን በሰንሰለት በማሰር እኛም እንደ አርበኛው አንዳርጋቸው ጽጌና በእስር ቤት የሚሰቃዩ ኢትዮጵያውን የቁም እስረኞች ነን የሚል ጥልቅ መልእክት አስተላልፈዋል። ብዙ መስራትና መጻፍ የሚችሉ እጆች፣ መናገር የሚችል አንደበት፣ የእውቀት ባለቤት የሆነ አእምሮ ታስረዋልና እኛም ወጣቶች እስረኞች ነን በሚል ውስጣዊ ስሜት ለስዓታት የኖርዌ ብርድና ቁር ሳይበግራቸው እጃቸውን በሰንሰለት በማሰር ድምጻቸውን ከፍ አድርገው አሰምተዋል።
DSC_0185DSC_0193DSC_0208DSC_0323

እንዲሁም ሰልፈኞቹ  የተለያዩ መፈክሮችን በመያዝ በታላቅ ድምጽና ስሜት ለኢንባሲው  አሰምተዋል።  ከአሰሟቸው  መፈክሮች መካከል ለአብነት “ UK, were is your citizen, Free Andrgachew Tsige, Andargachew is our icon of democracy, where is your action , stop discrimination among citizens, Yes, we are all Andrgachew Tsige, Brtain dont support terrirost regim in Ethiopia” የሚሉት ይገኙበታል::
ሰልፎኞችም የኢንግሊዝ  መንግሥት የነጻነት ታጋዩን አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን ከወያኔ እጅ እስካላወጡ  ድረስ ተቃውሞው በቀጣይ እስከ መጨረሻው ድረስ ከዚህ በበለጠ ቁጣና እልህ በተሞላበት ድምጻቸውን እንደሚያሰሙ ተናግረዋል።  በተመሳሳይም ለአንዳርጋቸው ያላችውን ፍቅርና ክብር በአደባባይ አስመሰክረዋል።
በመጨረሻም በድርጅቱ የተዘጋጀውን  ደብዳቤ በድርጅቱ ሊቀመንበር በአቶ ዮሃንስ ዓለሙ  አማካኝነት ለእንግሊዝ ኢምባሲ ተወካይ ጉዳዩ ትኩረት የሚሻና ጊዜ የማይሰጠው መሆኑን ለማሳሰብ ቢፈለጉም ተወካይ ሊመጣ ባለመቻሉ ደብዳቤው በበር ጠባቂው አማካኝነት እንዲደርሳቸው ተደርጓል። በተጨማሪም ደብዳቤውን በኢሜይል በድጋሚ እንደሚላክ ለሰልፈኞች አሳውቀዋል። ወደፊት በሚደረገው ተቃዉሞ ላይ ተወካይ መጥቶ እስካልተቀበለንና አቶ አንዳርጋቸው የደረሱበትን እስካላወቅን ድረስ ከኢንባሲው በር የማንቀሳቀስ መሆኑን ሁሉም በከፍተኛ ድምጽ አሰምተው ዝግጅቱ በተሳካ ሁኔታ ከቀኑ 15፡00 ተጠናቋል።

ዛሬም ነገም ሁላችንም አንዳርጋቸው ፅጌ ነን!!!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!
የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌ
source DCESON

Thursday, November 20, 2014

ከ400 በላይ ህዝብ የተፈናቀለበት መሬት በሙስና ተቸበቸበ

ከ400 በላይ ህዝብ የተፈናቀለበት መሬት በሙስና ተቸበቸበ

EU Human Rights Committee hearing on Andargachew Tsege's illegal capture...

Norway, Bergen: Discussion on Current Ethiopian Affairs

November 15, 2014
Democratic Change Support Organization in Norway, Bergen Branch will prepare a conference on 13 Dec 2014 In Bergen Norway.
Democratic Change Support Organization in Norway, Bergen meeting.

በሃብታሙ አያሌው ላይ የቀረበው ክስ ዝርዝር (እንደወረደ)

Filed under: News,News Feature | 
  • 89
     
    Share

habtamu ayalew
(ዘ-ሐበሻ) በእስር ላይ የሚገኘው ታዋቂው ወጣት ፖለቲከኛ ሃብታሙ አያሌው በመንግስት አቃቤ ሕግ የቀረበበት የክስ ቻርጅ በፍርድ ቤት ተሰምቷል:: ሙሉው የክስ ቻርጅ ለዘ-ሐበሻ አንባቢዎች ግንዛቤ ይረዳል በሚል እንደወረደ ቀርቧል::
habtamu ayalew
habtamu sp


habtamu ayalew2habt 1
habtamu ayalew 1habt1
hab 7habt8habt9habtamu ayalew 4
habt 12habt13habtamu ayalew 5
habt15habtamu ayalew 6
habtamu ayalew 7
habtamu 19

Friday, October 31, 2014

 | 

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የእስር ቅጣቱን በመቃወም ይግባኝ ሊጠየቅ ነው

  • 601
     
    Share
በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 16ኛ ወንጀል ችሎት ህዝብን ለአመፅ በማነሳሳትና ሀሰተኛ መረጃን በመስጠት በሚል ዐቃቤ ሕግ ክስ መስርቶበት የ3 ዓመት ፅኑ እስራት የተፈረደበት በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ይግባኝ እንደሚጠይቁ ጠበቃው አቶ አመሀ መኮንን አስታወቁ። ጠበቃው አክለውም፤ ውጤቱ ምንም ይሁን ምን ሕጉ እስከፈቀደው ድረስ ማንኛውንም መድረክ አሟጠን እንጠቀማለን ሲሉ ተናግረዋል። ይግባኝ እንደሚጠይቁ ጠቁመው ያም ሆኖ የተለየ ውጤት ካልተገኘ እስከሰበር ችሎት እንደርሳለን ብለዋል።
በተከሳሹ ላይ ፍርድ ቤቱ የጥፋተኝነት ብይን ከሰጠ በኋላ ስለምን የቅጣት ማቅለያ አላቀረባችሁም ተብሎ ከሰንደቅ ጋዜጣ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱም፤ በመርህ ደረጃ ጥፋተኛ መባል አልነበረበትም፤ አሁን ጉዳዩ ብዙ ዓመት የመታሰርና ትንሽ ዓመት የመታሰር ብቻ ሳይሆን በዋናነት ለቅጣት ቅነሳ መከራከሪያችን ለህግ ጥፋቱን የማመን ምልክት ስላለው አልፈለግንም።
Temesghen Desalegn (CPJ)cropped
አመፅን ለመቀስቀስ በመሰናዳት ወንጀል ተሳትፎ፤ ሕገ-መንግስቱንና ህገመንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ የሚያነሳሱ ፅሁፎችን በቀድሞዋ ፍትህ ጋዜጣ ላይ ሲያሰፍር ነበር በሚል የፌዴራሉ ዐቃቤ ሕግ ክስ የመሰረተበት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፤ ጥፋተኛ የተባለበት ግዙፍ ያልሆነ የማሰናዳት ወንጀል ሥር በ3 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ሲል ፍርድ ቤት ባሳለፍነው ሰኞ ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም የቅጣት ውሳኔውን አስተላልፏል።
ዐቃቤ ሕግ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 16ኛ ወንጀል ችሎት ሶስት ክሶችን በጋዜጠኛው ላይ አቅርቦ በሰውና በሰነድ ማስረጃዎች አስረድቷል። ተከሳሹም ከተከሰሰባቸው ወንጀሎች ነፃ ያወጡኛል ያላቸውን የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች ለፍርድ ቤቱ አቅርቦ የተከራከረ ቢሆንም፤ ችሎቱ የግራ ቀኙን መረጃ መርምሮ ጥቅምት 3 ቀን 2007 ዓ.ም ጥፋተኛ ነህ ብሎት እንደነበር ይታወሳል።
በዐቃቤ ሕግ የክስ ዝርዝር የተጠቀሱት ፍሬ ሀሳቦች መካከል በአንደኛው ክስ ሥር “ሞትን የማይፈሩ ወጣቶች” በሚል ርዕስ ነሐሴ 23 ቀን 2003 ዓ.ም ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በፃፈው ሀተታ ውስጥ ወጣቶች ለአብዮትና ለለውጥ እንዲነሳሱ በማድረግ፤ በአረቡ አለም ወጣቶች የነበራቸውን ሚና በመጥቀስ አሁን ያለውን ስርዓት ለመቀየር ወጣቶች ለአመፅ እንዲነሳሱ አድርጓል የሚል ነው።
በ2ኛ ክስ ስር የተዘረዘረው ሀሳብ ደግሞ “የሁለተኛ ዜግነት ህይወት በኢትዮጵያ እስከመቼ?” በሚል ርዕስ ሐምሌ 22 ቀን 2003 ዓ.ም በፍትህ ጋዜጣ ባወጣው ሀተታ ስር መንግስት በተለያዩ ክልሎች የጅምላ ጭፍጨፋ ፈፅሟል በማለት የአገሪቱን መንግስት ስም በማጥፋትና በሀሰት ወንጅሏል የሚል ክስ ተመስርቶበታል።
ዐቃቤ ሕግ 3ኛ ክስ አድርጎ ያቀረበው ደግሞ በመጋቢት 7 ቀን 2004 ዓ.ም በታተመችው ፍትህ ጋዜጣ ላይ “ሲኖዶሱና መጅሊሱ የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ማጥመቂያ” ሲል ባሰፈረው ፅሁፍ መንግስት የሃይማኖት ተቋማቱን ለፖለቲካዊ ዓላማ እየተጠቀመባቸው ስለመሆኑ በማተት የህዝብን እምነት እንዲሸረሸር አድርጓል ሲል ይከሰዋል።
ተከሳሹ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፤ ለፍርድ ቤቱ አቅርቧቸው በነበሩ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች አማካኝነት በጥቅሉ፤ የጋዜጠኝነት ተግባሩን እየተወጣ በመሆኑንና በዚህም ህገ መንግስቱ የሰጠውን ኀሰብን የመግለፅ ነፃነት ተጠቅሞ ሥራውን ማከናወኑን ባቀረባቸው የመከላከያ ምስክሮች ጭምር አስረድቷል።
ሆኖም የግራ ቀኙን ክርክር ሲመረምር የቆየው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 16ኛ ወንጀል ችሎት ጥቅምት 3 ቀን 2007 ዓ.ም ጥፋተኛ ማለቱን ተከትሎ ባሳለፍነው ሰኞ የቅጣት ውሳኔውን አስተላልፏል። በዚህም የውሳኔ ንባብ ወቅት ፍርድ ቤቱ እንዳለው፤ ምንም እንኳን ተከሳሹ ጥፋተኛ ቢባልም የቀረቡበት 3 ክሶች በአንድ ሃሳብ ሊጠየቅ የሚገባው ነው በሚል፤ በወንጀል ህጉ የመገፋፋትና ግዙፍ ያልሆነ የማሰናዳት ተግባር ወንጀል ብቻ ይቀጣ ማለቱን ተከትሎ ምንም አይነት የቅጣት ማቅለያ ባላቀረበው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላይ የ3 ዓመት ፅኑ እስራት ፈርዶበታል።
በተያያዘም አሳታሚው ማስተዋል የህትመትና ማስታወቂያ ኃ/የተ/የግ ማህበር ላይ ዐቃቤ ሕግ አቅርቦት የነበረው የንብረት ይወርስልኝ ጥያቄን ፍርድ ቤቱ ወደጎን በመተው የ10ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ጥሎበታል።
ምንጭ፦ zehabesha