Saturday, December 20, 2014
Thursday, December 11, 2014
Monday, December 8, 2014
Breaking News: 70 Ethiopian migrants drown off Red Sea coast of Yemen
December 7, 2014
(Reuters) – At least 70 Ethiopians drowned when a boat used by smugglers to transport illegal migrants to Yemen sank in the Red Sea in rough weather, security authorities in the western part of the country said on Sunday.

Human traffickers often use unseaworthy boats to smuggle African migrants to Yemen, seen as a gateway to wealthier parts of the Middle East, such as Saudi Arabia and Oman, and the West.
Security authorities in Taiz province said the small boat sank on Saturday due to high winds and rough seas off the country’s al-Makha port.
They said the boat was carrying 70 people, all of them Ethiopians.
Tens of thousands of migrants from Africa, the Middle East and beyond crowd into often unsafe boats each year and many drown.
In March, at least 42 illegal African migrants drowned in the Arabian Sea off the southern coast of Yemen.
source ECADF
Tuesday, December 2, 2014
Friday, November 28, 2014
የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌ የወጣቶች ክፍል አዘጋጅነት ታላቅ ሰላማዊሰልፍ በኖርዌይ ኦስሎ ተካሄደ!!!
የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌ የወጣቶች ክፍል አዘጋጅነት በዛሬው እለት ሀሙስ (November 27,2014) በኖርዌ ኦስሎ በእንግሊዝ ኢንባሲ ፊት በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከሩቅም ከቅርብም በአንድነት በመሰባሰብ ከቀኑ 13፡30 እስከ 15፡00 ስዓት ታላቅ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ አካሄዱ።
የሰልፉ ዋና አላማ የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሃፊና የሰባዊ መብት ተቆርቋሪ የሆኑት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በአንምባ ገነኑ የወያኔ ቡድን በህገ ወጥ መንገድ ታፍነውና ፍትህ ተነፍገው በእስር ቤት መታሰራቸውን ለመቃወም ሲሆን በሰልፉ ስፍራ የተገኙ ሰዎች ሁሉ አቶ አንዳርጋቸው ለዲሞክራሲ እና ሰብአዊ መብት መከበር ከወጣትነት ጀምሮ የታገለ ታላቅ የሰላም ምሳሌ፣ የፍትህ ተምሳሌት፣ የነጻነት በር ከፋች እንዲሁም አገራዊ ስሜት የተላበሰ አርበኛ እንጂ እስር፣ ድብደባና መሰቃየት የሚገባው ሰው አልነበረም በማለት ለእንግሊዝ መንግስት በኢንባሲው አማካኝነት ዜጋዋን ከአረመኔና ጨካኝ መዳፍ እንድትታደግና ፍትህ እንዲያገኝ በከፍተኛ ድምጽ አሳስበዋል።
ወጣቶች እጃቸውን በሰንሰለት በማሰር እኛም እንደ አርበኛው አንዳርጋቸው ጽጌና በእስር ቤት የሚሰቃዩ ኢትዮጵያውን የቁም እስረኞች ነን የሚል ጥልቅ መልእክት አስተላልፈዋል። ብዙ መስራትና መጻፍ የሚችሉ እጆች፣ መናገር የሚችል አንደበት፣ የእውቀት ባለቤት የሆነ አእምሮ ታስረዋልና እኛም ወጣቶች እስረኞች ነን በሚል ውስጣዊ ስሜት ለስዓታት የኖርዌ ብርድና ቁር ሳይበግራቸው እጃቸውን በሰንሰለት በማሰር ድምጻቸውን ከፍ አድርገው አሰምተዋል።
እንዲሁም ሰልፈኞቹ የተለያዩ መፈክሮችን በመያዝ በታላቅ ድምጽና ስሜት ለኢንባሲው አሰምተዋል። ከአሰሟቸው መፈክሮች መካከል ለአብነት “ UK, were is your citizen, Free Andrgachew Tsige, Andargachew is our icon of democracy, where is your action , stop discrimination among citizens, Yes, we are all Andrgachew Tsige, Brtain dont support terrirost regim in Ethiopia” የሚሉት ይገኙበታል::
ሰልፎኞችም የኢንግሊዝ መንግሥት የነጻነት ታጋዩን አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን ከወያኔ እጅ እስካላወጡ ድረስ ተቃውሞው በቀጣይ እስከ መጨረሻው ድረስ ከዚህ በበለጠ ቁጣና እልህ በተሞላበት ድምጻቸውን እንደሚያሰሙ ተናግረዋል። በተመሳሳይም ለአንዳርጋቸው ያላችውን ፍቅርና ክብር በአደባባይ አስመሰክረዋል።
በመጨረሻም በድርጅቱ የተዘጋጀውን ደብዳቤ በድርጅቱ ሊቀመንበር በአቶ ዮሃንስ ዓለሙ አማካኝነት ለእንግሊዝ ኢምባሲ ተወካይ ጉዳዩ ትኩረት የሚሻና ጊዜ የማይሰጠው መሆኑን ለማሳሰብ ቢፈለጉም ተወካይ ሊመጣ ባለመቻሉ ደብዳቤው በበር ጠባቂው አማካኝነት እንዲደርሳቸው ተደርጓል። በተጨማሪም ደብዳቤውን በኢሜይል በድጋሚ እንደሚላክ ለሰልፈኞች አሳውቀዋል። ወደፊት በሚደረገው ተቃዉሞ ላይ ተወካይ መጥቶ እስካልተቀበለንና አቶ አንዳርጋቸው የደረሱበትን እስካላወቅን ድረስ ከኢንባሲው በር የማንቀሳቀስ መሆኑን ሁሉም በከፍተኛ ድምጽ አሰምተው ዝግጅቱ በተሳካ ሁኔታ ከቀኑ 15፡00 ተጠናቋል።
ዛሬም ነገም ሁላችንም አንዳርጋቸው ፅጌ ነን!!!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!
የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌ
source DCESON
Friday, October 31, 2014
Wednesday, October 29th, 2014 | Posted by ዘ-ሐበሻ
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የእስር ቅጣቱን በመቃወም ይግባኝ ሊጠየቅ ነው
በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 16ኛ ወንጀል ችሎት ህዝብን ለአመፅ በማነሳሳትና ሀሰተኛ መረጃን በመስጠት በሚል ዐቃቤ ሕግ ክስ መስርቶበት የ3 ዓመት ፅኑ እስራት የተፈረደበት በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ይግባኝ እንደሚጠይቁ ጠበቃው አቶ አመሀ መኮንን አስታወቁ። ጠበቃው አክለውም፤ ውጤቱ ምንም ይሁን ምን ሕጉ እስከፈቀደው ድረስ ማንኛውንም መድረክ አሟጠን እንጠቀማለን ሲሉ ተናግረዋል። ይግባኝ እንደሚጠይቁ ጠቁመው ያም ሆኖ የተለየ ውጤት ካልተገኘ እስከሰበር ችሎት እንደርሳለን ብለዋል።
በተከሳሹ ላይ ፍርድ ቤቱ የጥፋተኝነት ብይን ከሰጠ በኋላ ስለምን የቅጣት ማቅለያ አላቀረባችሁም ተብሎ ከሰንደቅ ጋዜጣ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱም፤ በመርህ ደረጃ ጥፋተኛ መባል አልነበረበትም፤ አሁን ጉዳዩ ብዙ ዓመት የመታሰርና ትንሽ ዓመት የመታሰር ብቻ ሳይሆን በዋናነት ለቅጣት ቅነሳ መከራከሪያችን ለህግ ጥፋቱን የማመን ምልክት ስላለው አልፈለግንም።

አመፅን ለመቀስቀስ በመሰናዳት ወንጀል ተሳትፎ፤ ሕገ-መንግስቱንና ህገመንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ የሚያነሳሱ ፅሁፎችን በቀድሞዋ ፍትህ ጋዜጣ ላይ ሲያሰፍር ነበር በሚል የፌዴራሉ ዐቃቤ ሕግ ክስ የመሰረተበት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፤ ጥፋተኛ የተባለበት ግዙፍ ያልሆነ የማሰናዳት ወንጀል ሥር በ3 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ሲል ፍርድ ቤት ባሳለፍነው ሰኞ ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም የቅጣት ውሳኔውን አስተላልፏል።
ዐቃቤ ሕግ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 16ኛ ወንጀል ችሎት ሶስት ክሶችን በጋዜጠኛው ላይ አቅርቦ በሰውና በሰነድ ማስረጃዎች አስረድቷል። ተከሳሹም ከተከሰሰባቸው ወንጀሎች ነፃ ያወጡኛል ያላቸውን የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች ለፍርድ ቤቱ አቅርቦ የተከራከረ ቢሆንም፤ ችሎቱ የግራ ቀኙን መረጃ መርምሮ ጥቅምት 3 ቀን 2007 ዓ.ም ጥፋተኛ ነህ ብሎት እንደነበር ይታወሳል።
በዐቃቤ ሕግ የክስ ዝርዝር የተጠቀሱት ፍሬ ሀሳቦች መካከል በአንደኛው ክስ ሥር “ሞትን የማይፈሩ ወጣቶች” በሚል ርዕስ ነሐሴ 23 ቀን 2003 ዓ.ም ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በፃፈው ሀተታ ውስጥ ወጣቶች ለአብዮትና ለለውጥ እንዲነሳሱ በማድረግ፤ በአረቡ አለም ወጣቶች የነበራቸውን ሚና በመጥቀስ አሁን ያለውን ስርዓት ለመቀየር ወጣቶች ለአመፅ እንዲነሳሱ አድርጓል የሚል ነው።
በ2ኛ ክስ ስር የተዘረዘረው ሀሳብ ደግሞ “የሁለተኛ ዜግነት ህይወት በኢትዮጵያ እስከመቼ?” በሚል ርዕስ ሐምሌ 22 ቀን 2003 ዓ.ም በፍትህ ጋዜጣ ባወጣው ሀተታ ስር መንግስት በተለያዩ ክልሎች የጅምላ ጭፍጨፋ ፈፅሟል በማለት የአገሪቱን መንግስት ስም በማጥፋትና በሀሰት ወንጅሏል የሚል ክስ ተመስርቶበታል።
ዐቃቤ ሕግ 3ኛ ክስ አድርጎ ያቀረበው ደግሞ በመጋቢት 7 ቀን 2004 ዓ.ም በታተመችው ፍትህ ጋዜጣ ላይ “ሲኖዶሱና መጅሊሱ የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ማጥመቂያ” ሲል ባሰፈረው ፅሁፍ መንግስት የሃይማኖት ተቋማቱን ለፖለቲካዊ ዓላማ እየተጠቀመባቸው ስለመሆኑ በማተት የህዝብን እምነት እንዲሸረሸር አድርጓል ሲል ይከሰዋል።
ተከሳሹ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፤ ለፍርድ ቤቱ አቅርቧቸው በነበሩ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች አማካኝነት በጥቅሉ፤ የጋዜጠኝነት ተግባሩን እየተወጣ በመሆኑንና በዚህም ህገ መንግስቱ የሰጠውን ኀሰብን የመግለፅ ነፃነት ተጠቅሞ ሥራውን ማከናወኑን ባቀረባቸው የመከላከያ ምስክሮች ጭምር አስረድቷል።
ሆኖም የግራ ቀኙን ክርክር ሲመረምር የቆየው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 16ኛ ወንጀል ችሎት ጥቅምት 3 ቀን 2007 ዓ.ም ጥፋተኛ ማለቱን ተከትሎ ባሳለፍነው ሰኞ የቅጣት ውሳኔውን አስተላልፏል። በዚህም የውሳኔ ንባብ ወቅት ፍርድ ቤቱ እንዳለው፤ ምንም እንኳን ተከሳሹ ጥፋተኛ ቢባልም የቀረቡበት 3 ክሶች በአንድ ሃሳብ ሊጠየቅ የሚገባው ነው በሚል፤ በወንጀል ህጉ የመገፋፋትና ግዙፍ ያልሆነ የማሰናዳት ተግባር ወንጀል ብቻ ይቀጣ ማለቱን ተከትሎ ምንም አይነት የቅጣት ማቅለያ ባላቀረበው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላይ የ3 ዓመት ፅኑ እስራት ፈርዶበታል።
በተያያዘም አሳታሚው ማስተዋል የህትመትና ማስታወቂያ ኃ/የተ/የግ ማህበር ላይ ዐቃቤ ሕግ አቅርቦት የነበረው የንብረት ይወርስልኝ ጥያቄን ፍርድ ቤቱ ወደጎን በመተው የ10ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ጥሎበታል።
በተከሳሹ ላይ ፍርድ ቤቱ የጥፋተኝነት ብይን ከሰጠ በኋላ ስለምን የቅጣት ማቅለያ አላቀረባችሁም ተብሎ ከሰንደቅ ጋዜጣ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱም፤ በመርህ ደረጃ ጥፋተኛ መባል አልነበረበትም፤ አሁን ጉዳዩ ብዙ ዓመት የመታሰርና ትንሽ ዓመት የመታሰር ብቻ ሳይሆን በዋናነት ለቅጣት ቅነሳ መከራከሪያችን ለህግ ጥፋቱን የማመን ምልክት ስላለው አልፈለግንም።

አመፅን ለመቀስቀስ በመሰናዳት ወንጀል ተሳትፎ፤ ሕገ-መንግስቱንና ህገመንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ የሚያነሳሱ ፅሁፎችን በቀድሞዋ ፍትህ ጋዜጣ ላይ ሲያሰፍር ነበር በሚል የፌዴራሉ ዐቃቤ ሕግ ክስ የመሰረተበት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፤ ጥፋተኛ የተባለበት ግዙፍ ያልሆነ የማሰናዳት ወንጀል ሥር በ3 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ሲል ፍርድ ቤት ባሳለፍነው ሰኞ ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም የቅጣት ውሳኔውን አስተላልፏል።
ዐቃቤ ሕግ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 16ኛ ወንጀል ችሎት ሶስት ክሶችን በጋዜጠኛው ላይ አቅርቦ በሰውና በሰነድ ማስረጃዎች አስረድቷል። ተከሳሹም ከተከሰሰባቸው ወንጀሎች ነፃ ያወጡኛል ያላቸውን የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች ለፍርድ ቤቱ አቅርቦ የተከራከረ ቢሆንም፤ ችሎቱ የግራ ቀኙን መረጃ መርምሮ ጥቅምት 3 ቀን 2007 ዓ.ም ጥፋተኛ ነህ ብሎት እንደነበር ይታወሳል።
በዐቃቤ ሕግ የክስ ዝርዝር የተጠቀሱት ፍሬ ሀሳቦች መካከል በአንደኛው ክስ ሥር “ሞትን የማይፈሩ ወጣቶች” በሚል ርዕስ ነሐሴ 23 ቀን 2003 ዓ.ም ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በፃፈው ሀተታ ውስጥ ወጣቶች ለአብዮትና ለለውጥ እንዲነሳሱ በማድረግ፤ በአረቡ አለም ወጣቶች የነበራቸውን ሚና በመጥቀስ አሁን ያለውን ስርዓት ለመቀየር ወጣቶች ለአመፅ እንዲነሳሱ አድርጓል የሚል ነው።
በ2ኛ ክስ ስር የተዘረዘረው ሀሳብ ደግሞ “የሁለተኛ ዜግነት ህይወት በኢትዮጵያ እስከመቼ?” በሚል ርዕስ ሐምሌ 22 ቀን 2003 ዓ.ም በፍትህ ጋዜጣ ባወጣው ሀተታ ስር መንግስት በተለያዩ ክልሎች የጅምላ ጭፍጨፋ ፈፅሟል በማለት የአገሪቱን መንግስት ስም በማጥፋትና በሀሰት ወንጅሏል የሚል ክስ ተመስርቶበታል።
ዐቃቤ ሕግ 3ኛ ክስ አድርጎ ያቀረበው ደግሞ በመጋቢት 7 ቀን 2004 ዓ.ም በታተመችው ፍትህ ጋዜጣ ላይ “ሲኖዶሱና መጅሊሱ የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ማጥመቂያ” ሲል ባሰፈረው ፅሁፍ መንግስት የሃይማኖት ተቋማቱን ለፖለቲካዊ ዓላማ እየተጠቀመባቸው ስለመሆኑ በማተት የህዝብን እምነት እንዲሸረሸር አድርጓል ሲል ይከሰዋል።
ተከሳሹ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፤ ለፍርድ ቤቱ አቅርቧቸው በነበሩ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች አማካኝነት በጥቅሉ፤ የጋዜጠኝነት ተግባሩን እየተወጣ በመሆኑንና በዚህም ህገ መንግስቱ የሰጠውን ኀሰብን የመግለፅ ነፃነት ተጠቅሞ ሥራውን ማከናወኑን ባቀረባቸው የመከላከያ ምስክሮች ጭምር አስረድቷል።
ሆኖም የግራ ቀኙን ክርክር ሲመረምር የቆየው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 16ኛ ወንጀል ችሎት ጥቅምት 3 ቀን 2007 ዓ.ም ጥፋተኛ ማለቱን ተከትሎ ባሳለፍነው ሰኞ የቅጣት ውሳኔውን አስተላልፏል። በዚህም የውሳኔ ንባብ ወቅት ፍርድ ቤቱ እንዳለው፤ ምንም እንኳን ተከሳሹ ጥፋተኛ ቢባልም የቀረቡበት 3 ክሶች በአንድ ሃሳብ ሊጠየቅ የሚገባው ነው በሚል፤ በወንጀል ህጉ የመገፋፋትና ግዙፍ ያልሆነ የማሰናዳት ተግባር ወንጀል ብቻ ይቀጣ ማለቱን ተከትሎ ምንም አይነት የቅጣት ማቅለያ ባላቀረበው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላይ የ3 ዓመት ፅኑ እስራት ፈርዶበታል።
በተያያዘም አሳታሚው ማስተዋል የህትመትና ማስታወቂያ ኃ/የተ/የግ ማህበር ላይ ዐቃቤ ሕግ አቅርቦት የነበረው የንብረት ይወርስልኝ ጥያቄን ፍርድ ቤቱ ወደጎን በመተው የ10ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ጥሎበታል።
ምንጭ፦ zehabesha
Subscribe to:
Posts (Atom)